Tuesday, April 17, 2012


ሰላም ለእናንተ ይሁን ዮሐ 20-26
ዳግም ትንሣኤ

ከስምንት ቀን በኃላም ደቀመዝሙርቱ ደግመው በውስጥ ነበሩ፡፡ ቶማስም ከእነርሱ ጋር ነበረ ደጆች ተዘግተው ሳሉ ኢየሱስ መጣ :: በመካከላቸው ቆሞ ሰላም ለእናተ ይሁን አላቸው……

ዳግም ትንሣኤ፡- ማለት ለአስራ አንዱ ደቀ መዛሙርት ቶማስ ባለበት ለሁለተኛ ጊዜ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞቶ ከተነሰ በኃላ በግልጥ የታየበት ዕለት ሰለሆነ ቤተ ክርስቲያናችን ደግም ትንሣኤ በማለት ይህንን ዕለት ታከብረዋለች

ዳግም ትንሣኤ
-የቶማስ አለማመንና መጠራጠር ፍፁም ወደሆነና ወደ ታላቅ እምነት የተቀየረበት (ዩሐ20-27)
-በተዘጋው ቤት አምላካችን ገብቶ በእብራይስጥ ቋንቋ ‹‹ሻሎም›› ሰላም ለእናንተ ይሁን በማለት የደቀመዛሙርቱን ፍርሐት ወደ ልበ ሙሉነት የተቀየረበት ዕለት፡፡

በዚህ ባለንበ ዘመን ሁሉም ሰው ሰላም አጥቶአል
-የኑሮ ውድነት፣ የጤና ማጣት
ሁሉም ነገር ተለውጦአል ከሚሽከረከረው የሕይወት ዑደት ውስጥ ለመግባት ባለጠጋ ወይም ቆንጆሁን ፣አልያም ተማር፣ እንዲህ 
ካልሆንክ ዋጋ የለህም ወደሚል የኑሮ ስርዓት ገብተናል

የህይወት ዋጋው ገንዘብና ቆንጆነት ከሆነ ደሆችና በአካላቸው ላይ ጉዳት የደረሰባቸው ምን ይሁኑ ቅንነትና ታማኝነት ተረስተው ሰው ለቆዳው መጨነቅ ጀምሮል የዛሬውን ምስቅልቅል ኑሮ ይህ የተለወጠ ዋጋ ነው ገንዘብ እና እውቀት ሰላምን ሊያመጣ አይችልም ሰላም ግን እውነትና ገንዘብን ሊያመጣ ይችላል፡፡


ሰላማችን ማነው?

ሰላማችን ክርስቶስ ነው፡፡ ኤፌ( 2-14 )የጠብን ግድግዳ በደሙፈሰሽነት ያፈረሰ
-የተለያዩትን አንድ ያደረገ ጠላታችን ዲያብሎስን ወደጥልቁ የጣለ ወደ ቀደመ ርስታችን የመለሰን ሰለማችን ክርስቶስ ነው ፡፡
-በሁኔታዎች ሊበጠበጥና ሊታወክ የማችል እውነተኛ፣ ሰላም፣ ደስታ እና ጉስቁልና የማይለውጠው የሁል ጊዜ ሰላማችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡
-ክርስቶስ ማዕበል ቢመጣም ሰላም፣ ማዕበል ባይመጣም ሰላም፣ ሊቁ አባ ጊዬርጊስ ዘጋስጫ ምገድ የማይሰባብረው መርከባችን እርሱ ብሎ እንደተናገረው ሰዎች የሰጡንን ሰላም ሰዎች ሊወስዱት ይችላሉ እዚህጋ በአንዱ ተደስተን እዚያጋ ደግሞ በሌሎች ልናዝን እንችላለን ክርስቶስን ግን ሁል ጊዜ ሰላማችን ነው ::

መልእክት
አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞቶ ከተነሳ በኃላ የደቀመዛሙርቱን ፍርሐት በማስወገድ ሰላም ሰጥቶአችኃል፡፡
-የቶማስንም የመጠራጠር ሕይወት ወደ ፍፁም እምነት እንዲለወጥ አድርጎል፡፡ በዚህ ዘመን ሰላማችን የደፈረሰብን ሰላም የሚሰጠን ማነው? በማለት የተጨነቅን ፣ገንዘብ ሰላም ሊሰጠን አይችልም ፡፡ እውቀትም የተነጠቀው ሰላማችንን ሊመልስልን አይችልም፡፡ ሰላማችን ክርስቶስ ብቻ ነው እና በተዘጋው ማንነታችን ሁሉ ፡ በመካከላችን ቆሞ ሰላም ለአንተ ይሁን፣ ሰላም ለአንቺ ይሁን በማለት የተወሰደብንን ሰላም የሰላም አለቃ ፣የሰላም መገኛ ፣የሰላም አምላክ ሞትን ድል አድርጎ የተነሳው ጌታ ለደቀመዛሙርቱ ሰላምን እንደሰጠ ለሁላችንም ሰላሙን ይስጠን ሰላሙን ያድለን ሰላሙን ያብዛልን አሜን

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል

No comments:

Post a Comment